ምን ያህሎቻችን የአስራ ሦስቱን ወራት ስያሜ እናውቃለን?
መልካም ንባብ
1/14
መልካም ንባብ


<<መስከረም>>
መስከረም ማለት ክረምቱ አለፈ ማለት ነው።
መስ - ማለት አለፈ ሲሆን
ከረመ - ማለት ደግሞ ክረምት ነው።
መነሻ ቃል ፦ መስ እና ከረመ 2/14

መስከረም ማለት ክረምቱ አለፈ ማለት ነው።
መስ - ማለት አለፈ ሲሆን
ከረመ - ማለት ደግሞ ክረምት ነው።
መነሻ ቃል ፦ መስ እና ከረመ 2/14
<<ጥቅምት>> 
ጥቅምት ማለት ጠቃሚ ጊዜ (ስራ የሚሰራበት ጊዜ) ማለት ነው።
መነሻ ቃል ፦ ጠቀመ 3/14

ጥቅምት ማለት ጠቃሚ ጊዜ (ስራ የሚሰራበት ጊዜ) ማለት ነው።
መነሻ ቃል ፦ ጠቀመ 3/14
<<ኅዳር>> 
ሕዳር ማለት ማደር ማለት ነው።
ገበሬው ለአስመራ ጊዜ ማሳ ውስጥ ለጥበቃ ማደሩን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ኀደረ 4/14

ሕዳር ማለት ማደር ማለት ነው።
ገበሬው ለአስመራ ጊዜ ማሳ ውስጥ ለጥበቃ ማደሩን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ኀደረ 4/14
<<ታኅሳስ>>
ታሕሳስ ማለት መመርመር ማለት ነው።
ገበሬው በመኸር ወቅት ሰብል መመርመሩን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ኀሠሠ 5/14

ታሕሳስ ማለት መመርመር ማለት ነው።
ገበሬው በመኸር ወቅት ሰብል መመርመሩን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ኀሠሠ 5/14
<<ጥር>>
ጥር ማለት ጠረረ፣ነጻ (ብልጭ አለ) ማለት ነው።
የፀሐይን ግለት ወቅት ያሳያል።
መነሻ ቃል ፦ ነጠረ 6/14

ጥር ማለት ጠረረ፣ነጻ (ብልጭ አለ) ማለት ነው።
የፀሐይን ግለት ወቅት ያሳያል።
መነሻ ቃል ፦ ነጠረ 6/14
<<የካቲት>>
የካቲት ማለት መክተቻ ማለት ነው።
የእህል መክተቻ ወቅት መሆኑን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ከቲት 7/14

የካቲት ማለት መክተቻ ማለት ነው።
የእህል መክተቻ ወቅት መሆኑን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ከቲት 7/14
<<መጋቢት>>
መጋቢት ማለት መመገብ ማለት ነው።
ገበሬው በጎተራው የከተተውን የሚመገብበት ወቅት መሆኑን
ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ መገበ 8/14
መጋቢት ማለት መመገብ ማለት ነው።
ገበሬው በጎተራው የከተተውን የሚመገብበት ወቅት መሆኑን
ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ መገበ 8/14
<<ሚያዝያ>>
ሚያዝያ ማለት ጎለመሰ፣ ጎበዘ (ሚስት ፈለገ) ማለት ነው።
የሰርግ ወር መሆኑን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ መሐዘ 9/14

ሚያዝያ ማለት ጎለመሰ፣ ጎበዘ (ሚስት ፈለገ) ማለት ነው።
የሰርግ ወር መሆኑን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ መሐዘ 9/14
<<ግንቦት>>
ግንቦት ማለት ገነባ ፣ ሠራ ፣ ቆፈረ ፣ ሰረሰረ ማለት ነው።
ገበሬው ለእርሻ መሬቱ መዘጋጀቱን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ገነበ 10/14
ግንቦት ማለት ገነባ ፣ ሠራ ፣ ቆፈረ ፣ ሰረሰረ ማለት ነው።
ገበሬው ለእርሻ መሬቱ መዘጋጀቱን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ገነበ 10/14
<<ሰኔ>>
ሰኔ ማለት የሚያምር ነገር ማለት ነው።
ገበሬው ዘርቶ መሬቱ ማማሩን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ሰነየ 11/14

ሰኔ ማለት የሚያምር ነገር ማለት ነው።
ገበሬው ዘርቶ መሬቱ ማማሩን ያመለክታል።
መነሻ ቃል ፦ ሰነየ 11/14
<<ሐምሌ>>
ሐምሌ ማለት መልቀም ማለት ነው።
ገበሬው መልቀሙን ያመለክታል። (በተለይ ለጎመን)
መነሻ ቃል ፦ ሐመለ 12/14

ሐምሌ ማለት መልቀም ማለት ነው።
ገበሬው መልቀሙን ያመለክታል። (በተለይ ለጎመን)
መነሻ ቃል ፦ ሐመለ 12/14
<<ነሐሴ>>
ነሐሴ ማለት ማቅለል (መተው) ማለት ነው።
የክረምቱን መቅለል ያሳያል።
መነሻ ቃል ፦ አናሕስየ 13/14

ነሐሴ ማለት ማቅለል (መተው) ማለት ነው።
የክረምቱን መቅለል ያሳያል።
መነሻ ቃል ፦ አናሕስየ 13/14
<<ጳጉሜ>>
ጳጉሜ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው።
ተጨማሪ ወር መኖሩን ያመለክታል።(የግሪክ ቃል ነው)
መነሻ ቃል ፦ ኤጳጉሚኖስ 14/14

ጳጉሜ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው።
ተጨማሪ ወር መኖሩን ያመለክታል።(የግሪክ ቃል ነው)
መነሻ ቃል ፦ ኤጳጉሚኖስ 14/14
Retweet It
