
የመደነቅ ሰፊ ብቃት ነበራት። እነዚህ ኢትዮጵያውያኑ የንጉሣውያን ቤተሰቦች ስማቸው ምድር ላይ ተተክሎ መቅረት እንደሌለበት ያስቡ ነበር፡፡ በሥነ ፍጥረት በእጅጉ በመማረክ ይልቁኑ በምሽቱ ሰማይ ላይ የተለያየ ቅርጽ እየሠሩ የዕንቁ ፈርጥ መስለው -
በሰማይ ላይ እያበሩ እያብረቀረቁ የሚታዮትን ከዋክብት በጥንቃቄ ያስተውሉ ነበር፡፡ ይህ ዝናቸው እስከ ግሪክ ተሰምቶላቸው ስለነበር ግሪካውያኑ በኢትዮጵያውያኑ ንጉሣውያን ቤተሰቦች በመደነቅ ብዙ ማይቶሎጂዎችን ስለእነርሱ ይናገሩ ነበር፡፡
ከነዚያ ከሚመለከቷቸው ሕብረተ ከዋክብት ውስጥም ሦስቱን ንጉሥ ሴፌውስ፣ ንግሥት ካሲዮፒያና ልዕልት አንድሮሜዳ በስማቸው እንዲሰየምላቸው አድርገዋል፡፡ ይህ ታሪክ የሚታወቀው በእኛ ብቻ ሳይሆን በስነ ከዋክብት ጥናት ታላቅ ደረጃ ላይ በደረሱት -
በጥንታውያን ግሪኮችና ዛሬም ባለው የሥነ ከዋክብት የሳይንስ ጥናት ጭምር ነው፡፡
በ2ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ግሪካዊው የሥነ ከዋክብት ተመራማሪ ፕቶሎሚ ከመዘገባቸው 48 ሕብረተ ከዋክብት ውስጥ ሦሥቱ በኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ካሲዮፒያ፣
በ2ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ግሪካዊው የሥነ ከዋክብት ተመራማሪ ፕቶሎሚ ከመዘገባቸው 48 ሕብረተ ከዋክብት ውስጥ ሦሥቱ በኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ካሲዮፒያ፣
በኢትዮጵያዊው ንጉሥ ሴፌውስና በኢትዮጵያዊቷ ልዕልት አንድሮሜዳ ስም ነበር፡፡
ይህ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሕብረተ ከዋክብትን በመሰየም ያደረገችው ታላቅና ገናና ሥራ የማይካድ እውነት ነውና እጅግ በበርካቶች ተመራማሪዎችና ምርጥ ሳይንቲስቶች
ይህ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሕብረተ ከዋክብትን በመሰየም ያደረገችው ታላቅና ገናና ሥራ የማይካድ እውነት ነውና እጅግ በበርካቶች ተመራማሪዎችና ምርጥ ሳይንቲስቶች
የተዋቀረው የዓለም ዐቀፉ አስትሮኖሚ ኅብረት ለዚህ ድንቅ ታሪካችን ዕውቅናን በከፍተኛ ደረጃ በመስጠት ከመዘገባቸው 88 ሕብረተ ከዋክብትን ሦስቱ በንግሥት ካሲዮፒያ፣ በንጉሥ ሴፌውስና በልዕልት አንድሮሜዳ ስም ነው፡፡
ምንጭ- አንድሮሜዳ(መፅሐፍ) በዶ/ር ሮዳስ ታደሰ አና ዶ/ር ጌትነት ፈለቀ